በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በስዊድን አንድ ግለሰብ ት/ቤት ውስጥ በከፈተው ተኩስ 11 ሞቱ


በስዊድን ኦሬብሮ በሚገኘው ሪዝበርግስካ ትምህርት ቤት 11 ሰዎች ሕይወታቸውን ማጣታቸው ተከትሎ ሀዘንተኞች አበባዎችን እና ሻማዎችን በማስቀመጥ ሃዘናቸውን እየግለጽ፣ ስዊድን እአአ የካቲት 5/2025
በስዊድን ኦሬብሮ በሚገኘው ሪዝበርግስካ ትምህርት ቤት 11 ሰዎች ሕይወታቸውን ማጣታቸው ተከትሎ ሀዘንተኞች አበባዎችን እና ሻማዎችን በማስቀመጥ ሃዘናቸውን እየግለጽ፣ ስዊድን እአአ የካቲት 5/2025

በስዊድን አንድ ግለሰብ በጎልማሶች ትምህርት ቤት ውስጥ በከፈተው ተኩስ ግለሰቡን ጨምሮ 11 ሰዎች ሕይወታቸውን ሲያጡ ሌሎች አምስት ሰዎች ደግሞ ክፉኛ ተጎድተዋል ተብሏል።

ፖሊስ ግለሰቡ ድርጊቱን ለብቻው መፈጸሙን ገልጾ፣ የትምህርት ቤቱ ተማሪ ይሆን እንደሁ ወይም ምን እንዳነሳሳው አላሳወቅም።

የጅምላ ግድያው በስዊድን ታሪክ የከፋው እንደሆነ ተነግሯል።

ግድያው የተፈጸመው ከስቶክሆልም ወጣ ብሎ በሚገኝና ለጎልማሶች የአንደኛና የሁለተኛ ደርጃ ትምህርት እንዲሁም ለስደተኞችና ለሌሎችም የቋንቋና የሙያ ትምህርት በሚስጥበት ቅጥር ግቢ ውስጥ ነው።

ስዊድን ውስጥ በትምህርት ተቋማት በመሣሪያ የሚፈጸም ግድያ እምብዛም አይስተዋልም።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG