ያውንዴ —
በካሜሩን የሰሜናዊ ክልል አስተዳዳሪ ሚዲያዋ ባከሪ መግለጫ መሠረት፥ ሁለት ወጣት አጥፍቶ ጠፊዎች ናቸው ትላንት ከመሸ ከናይጄሪያ ቦርኖ ግዛት ድንበር አቋርጠው የገቡት፡ አንደኛው የታጠቀውን ፈንጂ ወጣቶች ተሰብስበው ፊልም በሚያዩበት ስፍራ ሲተኩስ ሁለተኛው መስጊድ ውስጥ አፈንድቷል ሲሉም አስረድተዋል።
ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።