በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በሱዳን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ የተሳተፉ እየታደኑ ናቸው


በመፈንቅለ መንግሥት ሙከራው የተሳተፉ ተጨማሪ መኮንኖችን የፀጥታ ኃይሎች እያደኑ ናቸው ሲል የሱዳን ገዢ ወታደራዊ ምክር ቤት ቃል አቀባይ አስታወቁ።

ትናንት ካከሸፍነው የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በኋላ መሪውን ጨምሮ ቢያንስ አስራ ስድስት መኮንኖች በቁጥጥር ሥር ውለዋል ሲሉ የገዢው ቡድን ቃል አቀባዩ ሌተና ጀነራል ጋማል ኦማር በመግለጫቸው አስታወቀዋል።

የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ የተደረገው ከአፍሪካ ዲሞክራሲ ሰልፈኞች ተወካዮች ስምምነት በሚፈረምበት ዋዜማ በሆነው ወሳኝ ወቅት ላይ ነው ሲሉ ቃል አቀባዩ አክለዋል።

ባለፈው ሳምንት የሱዳን የጦር ሰራዊት እና አፍሪካ ዲሞክራሲው ጥምረት ምርጫ እስከሚደራጅ ለሦስት ዓመት ያህል በጋራ ምክር ምክር ቤት ሊያስተዳድሩ መስማማታቸው ይታወሳል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG