በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኢትዮ­­‑አሜሪካዊው ምሁር በትረምፕ ንግግር ላይ


ፕሮፌሰር መሐመድ አባጀበል
ፕሮፌሰር መሐመድ አባጀበል

ኢሚግራንቶች ለአሜሪካ ሸክም ሳይሆኑ ሃብት ናቸው ሲሉ የቴክሳሷ ዳላስ ውስጥ የምጣኔ ኃብት ምሁርና ፕሮፌሰር የሆኑት ዶ/ር መሐመድ ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል።

ኢሚግራንቶች ለአሜሪካ ሸክም ሳይሆኑ ሃብት ናቸው ሲሉ የቴክሳሷ ዳላስ ውስጥ የምጣኔ ኃብት ምሁርና ፕሮፌሰር የሆኑት ዶ/ር መሐመድ አባጀበል ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል።

“በአንፃራዊ ሁኔታ የፕሬዚዳንት ትረምፕ የትናንት አቀራረብ ጥሩ ነበር” ብለዋል ትውልደ ኢትዮጵያ አሜሪካዊ ምሁርና ፖለቲከኛው ዶ/ር መሐመድ።

ዲቪ ሎተሪ በፕሬዚዳንት ትረምፕ ጥያቄ መሠረት ይቀር ይሆን እንደሆነ ፕሮፌሰር መሐመድ ሲጠየቁ ከዘጠኝ ወራት በኋላ በሚካሄደው የአማካይ ጊዜ የተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ዴሞክራቶቹ አንዱን ወይም ሁለቱንም የምክር ቤቱን ክንፎች ከተቆጣጠሩ ይሠረዛል ብለው እንደማያስቡ አመልክተው አሁን ባለው ሁኔታ ውስጥ በአሜሪካ ፖለቲካ ውስጥ ማንኛውም ነገር የሚሸጥ ነውና የተሻለ የሚሉት መደራደሪያ ከቀረበላቸው ምናልባት ዴሞክራቶቹ እጅ ሊሰጡ ይሆናል የሚል ሃሣብ እንዳላቸው ገልፀዋል።

የአሜሪካ የአክስዮን ገበያዎች ታይተው የማይታወቁ ጣሪያዎችን መንካት የነጋዴው ትረምፕ ወደ መንበረ ፕሬዚዳንቱ የመዝለቃቸው የገበያው ሥነ‑ልቦና ውጤት ሊሆን ይችላል ብለው እንደሚገምቱም ዶ/ር መሐመድ ተናግረዋል።

ከዶ/ር መሐመድ አባጀበል ጣሂሮ ጋር የተደረገውንም ሙሉ ቃለ‑ምልልስ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

ኢትዮ­­‑አሜሪካዊው ምሁር በትረምፕ ንግግር ላይ
please wait

No media source currently available

0:00 0:24:09 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG