ዩናይትድ ስቴትስ ለምርጫ እየተዘጋጀች ባለችበት ወቅት 'ስቴት ኦፍ ዩኒየን' የተሰኘውን የአሜሪካንን የዛሬ ሁኔታ የሚዳስስ ዓመታዊ ንግግራቸውን ዛሬ ምሽት የሚያደርጉት የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን፣ ስለ ኢኮኖሚ አያያዛቸው፣ የሥነ-ተዋልዶ መብት፣ ሥደት እና በዩክሬን እና በጋዛ ስለሚካሄደው ጦርነት ያነሳሉ ተብሎ ይጠበቃል። የ81-ዓመቱ ባይደን፣ ንግግሩን ለሁለተኛ የሥልጣን ዘመን በአካል እና በአይምሮ ብቁ መሆናቸውንም ለማሳየት ይጠቀሙበታል ተብሏል።
የአሜሪካ ድምፅ የዋይት ኃውስ ዘጋቢ አኒታ ፓውል ከዋሽንግተን ዲሲ ያደረሰችንን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
መድረክ / ፎረም