በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኮቪድ - 19 በሶማሌ ክልል

ጂግጂጋ
ጂግጂጋ

በሶማሌ ክልል ዛሬም ተጨማሪ የኮሮናቫይረስ ተጠቂዎች ተገኝተዋል። እስካሁን በክልሉ የኮሮናቫይረስ የተገኘባቸው 6 ሰዎች ሁሉም የውጭ የጉዞ ታሪክ ያላቸውና በለይቶ ማቆያ ውስጥ ያሉ ናቸው። ይሁንና በለይቶ ማቆያ ሳይገቡ የድንበር ጥበቃውን አልፈው ከኅብረተሰቡ ጋር የተቀላቀሉ አሉ ሲሉ ነዋሪዎች ስጋታቸውን ለቪኦኤ ገልጸዋል።

የክልሉ መንግሥት በበኩሉ ከፌደራል መንግስት ጋር በመተባበር አስፈላጊውን ጥበቃ እያደረገ መሆኑን ገልፆ ይሁንና ከድንበሩ ስፋት አንጻር ክፍተቶች ሊኖሩ ይችላሉ ብሏል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

ኮቪድ - 19 በሶማሌ ክልል
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:53 0:00


This item is part of
XS
SM
MD
LG