በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሶማሌ ላንድ ድርቅ ሊቀጥል እንደሚችል ተጠቆመ


የኖርዌይ የስደተኞች ምክር ቤት እንዳመለከተው የሶማሌ ላንድ ድርቅ ሊቀጥል እንደሚችል፣ ሰባት መቶ ሃያ አምስት ሺህ ሰው በረሃብ ሊመታ እንደሚችል ስጋቱን አሰምቷል።

በሶማልያ የ/ኤንአርሲ/ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቪችተር ሞሰስ በሰጡት መግለጫ በሚቀጥሉት ሁለት ወራት በቂ ዝናብ ስለማይጥል፣ ጨርሶ ላይዘንብም ስለሚችል ቀድሞም በምግብ ዕጥረት የተጎዱት ብዙ ሺህ ሴቶችና ህፃናት ይብሱን ሊጎዱ እንደሚችሉ ተናግረዋል።

ዓለምቀፉ ማኅበረሠብ አንድ ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ዶላር እንዲለግስ ጥሪ አሰምተዋል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG