በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሶማሌ ክልል መንግስት ካቢኔ አስቸኳይ ስብስባ


የሶማሌ ክልል መንግስት ካቢኔ ዛሬ ከሰዓት ባካሄደውሶማሌ የሚበዛባቸው ሶስቱን አወዛጋቢ ቀበሌዎች ወደሶማሌ ክልል እንዲዛወሩ ወስኗል::

ካቢኔው ማምሻውን ባወጣው ባለ8 ነጥብ መግለጫ በ2004ዓም ሶስቱ ቀበሌዎች ማለትም ገርበኢሴ; አዳይቱና ኡንዱፎ አብዛኛው ነዋሪያቸው ሶማሌ ሆኖ እያለ ወደአፋር ክልል እንዲካለሉ በወቅቱ የነበሩ አመራሮች የወሰኑት ውሳኔ የሀገሪቱን ህጎች የጣሰ በመሆኑ ከአሁን በሁዋላ እንደማይቀበለው አስታውቋል::

የአፋር ክልል የእነኚህን ቀበሌዎች ነዋሪዎች ፍላጎት ማሟላት አልቻለም ያለው መግለጫው መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እና የፌደራል መንግስት የነዋሪዎችን መሰረታዊ ፍላጎቶች በማሟላት ረገድ የበኩላቸውን እንዲያደርጉ ጠይቋል::

ሶስቱን ቀበሌዎች የሶማሌ ክልል የፀጥታ ሃይል ከፌደራል መንግስት ጋር በመተባበር ፀጥታቸውን እንዲያስከብር ያዘዘው መግለጫው የክልሉ የፀጥታ ሃይሎች ከክልሉ ወሰን ሳይወጡ ድንበር አካባቢ ያለውን ፀጥታ እንዲያጠናክሩም አዟል::

ስለመግለጫው ያላቸውን አስተያዬት የጠቅኳቸው የአፋር ክልል የመንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊው አቶ አህመድ ካሎይታ ስለመግለጫም ምንም መረጃ አንደሌላቸውና ክልሉ ወደፊት አቋሙን እንደሚያሳውቅ ገልፀውልናል::

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG