በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አዲሱ የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነት አፍሪካን በቴክኖሎጂና በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ያደርጋታል


የፓሪስ የአየር ንብረት ስምምነት አፍሪካ በቴክኖሎጂ አጠቃቀሟ እመርታ ልታገኝበት የምትችልበትን እድል እንደሰጣት ተነገረ።

የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትላቸውን ፈተናዎች ለመቋቋም የሚያስችል የገንዘብ አቅምም ለአህጉሪቱ እንዳስገኘላት ተጠቁሟል።

የፓሪስ ስምምነት ተግባራዊ የሆነበት ፍጥነት ምክንያት የሰው ልጅ በዚህች ምድር ላይ በጋራ ለመኖር ያለው ቁርጠኝነት መስክር ነው ተብሏል።

ዛሬ በአዲስ አበባ በሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስብሰባ ማዕከል የተከፈተው ስድስተኛው የአየር ንብረት ለውጥና ልማት በአፍሪካ ጉባዔ ዋና ርዕሱ ያደረገው

″የፓሪስ ስምምነት ለአፍሪካ ምን ይዟል?″ የሚል ነው፡፡

አዲሱ የፓሪስ ስምምነት የበካይ ጋዞችን ልቀት የመቆጣጠሪያ ስልቶችን ከመፍጠር ባሽገር ቀጣይ ልማት እንዳይቋረጥ ያረጋገጣል፡፡

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

አዲሱ የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነት አፍሪካን በቴክኖሎጂና በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ያደርጋታል
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:56 0:00

XS
SM
MD
LG