በአንዳንድ የኦሮምያ እና የሲዳማ ክልል አዋሳኝ አከባቢዎች የሰው ሕይወት የጠፋበት ግጭት መፈጠሩን የገለፀው የሲዳማ አንድነት ፓርቲ - ፌዴራል መንግሥት መፍትሔ እንዲፈልግና ግጭቱን በአፋጣኝ እንዲያስቆም ጥሪ አቅርቧል።
በሰሞኑ ግጭት ሰባት ሰዎች መገዳላቸውንና 17 መቁሰላቸውንም ፓርቲው ትናንት በሃዋሳ ከተማ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ አስታውቋል። ችግሩ ሁለቱ ሕዝቦች ባሏቸዉ ባሕላዊ የግጭት መፍቻ ዘዴዎች ሊቀረፍ እንደሚችልም ጠቅሷል።
ግጭቱን በተመለከተ ከሲዳማ እና ከኦሮሚያ ክልል መንግሥታት የተሰጠ መግለጫም ሆነ አስተያየት ባይኖርም - የፓርቲውን መግለጫ የሃዋሳው ዘጋቢያችን ዮናታን ዘብዴዎስ ተከታትሎታል።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ጁላይ 26, 2024
የኢትዮጵያውያኑ ባህላዊ ማዕድ እና አብሮነት ታዛ - በሚልዋኪ
-
ጁላይ 26, 2024
የፕሬዝደንት ጆ ባይደን ንግግር
-
ጁላይ 23, 2024
አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን በኮዲንግ ሞያ የማብቃት መርሐ ግብር ይፋ ኾነ
-
ጁላይ 22, 2024
የነዋሪዎች አስተያየት በፕሬዝደንት ባይደን ውሳኔ ላይ
-
ጁላይ 18, 2024
ጄ. ዲ. ቫንስ “አሜሪካ ትቅደም” መሪ ቃላቸው እንደሆነ አስታወቁ