በአንዳንድ የኦሮምያ እና የሲዳማ ክልል አዋሳኝ አከባቢዎች የሰው ሕይወት የጠፋበት ግጭት መፈጠሩን የገለፀው የሲዳማ አንድነት ፓርቲ - ፌዴራል መንግሥት መፍትሔ እንዲፈልግና ግጭቱን በአፋጣኝ እንዲያስቆም ጥሪ አቅርቧል።
በሰሞኑ ግጭት ሰባት ሰዎች መገዳላቸውንና 17 መቁሰላቸውንም ፓርቲው ትናንት በሃዋሳ ከተማ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ አስታውቋል። ችግሩ ሁለቱ ሕዝቦች ባሏቸዉ ባሕላዊ የግጭት መፍቻ ዘዴዎች ሊቀረፍ እንደሚችልም ጠቅሷል።
ግጭቱን በተመለከተ ከሲዳማ እና ከኦሮሚያ ክልል መንግሥታት የተሰጠ መግለጫም ሆነ አስተያየት ባይኖርም - የፓርቲውን መግለጫ የሃዋሳው ዘጋቢያችን ዮናታን ዘብዴዎስ ተከታትሎታል።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ማርች 29, 2024
ሕገ ወጥ ሰፈራ በባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ላይ ስጋት መፍጠሩ ተገለጸ
-
ማርች 28, 2024
ሠላሳ ዓመታት ያለፉት የኢትዮጵያ የሥነ ሕዝብ ፖሊሲ
-
ማርች 28, 2024
በጋቦን ብሔራዊ ምክክር ሊጀመር ነው
-
ማርች 28, 2024
በኢየሩሳሌም የሚገኙ የጋዛ ሆስፒታል ታማሚዎች ስጋት ገብቷቸዋል
-
ማርች 28, 2024
በተጠናከረው የሩሲያ የሚሳዬል ጥቃት ዩክሬናውያን የአሜሪካን ርዳታ ይሻሉ
-
ማርች 28, 2024
አማራ ክልል ለትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር መግለጫ ምላሽ ሰጠ