በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

"ሠንሰለት" - አዲስ ተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማ


የሰንሰለት ቴሌቭዥን ድራማ ደራሲና ዳይሬክተር ተመስገን አፈወርቅ እና ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ለገሰ
የሰንሰለት ቴሌቭዥን ድራማ ደራሲና ዳይሬክተር ተመስገን አፈወርቅ እና ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ለገሰ

"የተለያዩ ታሪኮች ተሰናስለው አንድ ቦይ ውስጥ የሚፈሱበት መንገድ ነው። ኢትዮጵያና እዚህ ያለውን ሕብረተሰብ በአንድ ታሪክ ውስጥ እየገመደ የሚራመድ ረዥም ፊልም ነው።" - ተመስገን አፈወርቅ የተከታታይ ፊልሙ ደራሲና ከዳይሬክተሮቹ አንዱ።

በቅርቡ ለተመልካቾች ማክሰኞ ምሽት የተዋወቀ ተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማ ነው - ሰንሰለት።

ታዋቂና አዳዲስ ተዋናዮች የተሳተፉበትና ቀጣይ ነውና ወደፊትም የሚሳተፉበት፤ የሁለት ዓለም ሕይወት ሊያስተሳስር የታለመ ድራማ ነው።

በዩናይትድ ስቴትስ ተሰርቶ ወደ ኢትዮጵያ ሲሰራጭ የመጀመሪያው እንደሚሆን የተነገረለት የተከታታይ ፊልም ሥራ የራሱን ታሪክ የጻፈም ይመስላል።

ከዋሽንግተን ዲሲ ወጣ ብላ በምትገኘው የሲልቨርስፕሪንግ ከተማ በይፋ የተዋወቀበትን ሥነ ሥርዓት ተንተርሶ የተሰናዳ ዘገባ ቀዳሚው ነው።

የሙዚቃና የድምፅና የምስል አቀናባሪዎችንና ሌሎች አጋዥ የፊልም ሞያተኞችን ጨምሮ ከሠላሳ በላይ ሰዎች የተሳተፉበት ተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማ ደራሲና ዳይሬክተር ተመስገን አፈወርቅ እና እንዲሁም ሌላው የፊልሙ ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ለገሰ ጋር ያደረግነው ቆይታ ምጥን የመጀመሪያ ክፍልም ዘገባውን ይከተላል።

የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

"ሠንሰለት" - አዲስ ተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማ
please wait

No media source currently available

0:00 0:12:21 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG