በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በታላቁ ሩጫ የተሳተፉ አባሎቼ ታሠሩ ሲል ሰማያዊ ፓርቲ ከሰሰ


please wait

No media source currently available

0:00 0:04:52 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

የትላንት በስቲያውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን መታሰቢያ ተንተርሶ በተሠናዳው ታላቁ ሩጫ “ሃሳባቸውን ለመግለጥ” የወጡ ያላቸው አባሎቹ ለእስር ተዳረጉ ሲል፤ ሰማያዊ ፓርቲ ወነጀለ።

ይበልጡን የፓርቲው አባልና የአመራር አባል የሆኑ ወጣት ሴቶች የሚገኙባቸው በርካቶች አሁንም በእስር ላይ እንደሚገኙ ነው፤ ሰማያዊ ፓርቲ ያስታወቀው።

በእንቅስቃሴው በመሳተፋቸው ብቻ የደምብ ልብስ በለበሱ ፖሊሶችና እንዲሁም የሲቪል ልብስ በለበሱ የደህንነት ሠራተኞች ለአጭር ጊዜ ተይዘው ከቆዩ በኋላ፥“ሁከትና ሽብር እያነሳሳችሁ፤” የሚል ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸው መለቀቃቸውን የፓርቲው የሴቶች ጉዳይ ምክትል ኃላፊ ወ/ሪት ኢየሩሳሌም ተሥፋው።
XS
SM
MD
LG