በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሩሲያ ምርመራ ጋዜጠኛው ከቁም እስር ነፃ ሆነ


የምርመራ ጋዜጠኛው ኢቫን ጋሉኖቭ ከቁም እስርነት ነፃ ሆኗል። ባለሥልጣኖች የታሰረበትን ምክንያት እየመረመሩ ነው ሲሉ የሩስያ የአገር አስተዳደር ሚኒስትር ቭላዲሚር ኮሎኮልሰቭ ተናግረዋል።

ኮሎኮልሰፍ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ጋዜጠኛውን ያሰረው ፖሊስ ከሥራ መታገዱን ገልፀዋል። ኢቫን ጋሉኖቭ ላይ የተደረገው የአሻራ፣ የሥነ ፍጥረታዊ፣ የወንጀልና የዘረመል ምርመራ በወንጀል ተግባር መሰማራቱን የሚያሳይ ማስረጃ ስላላሳዩ ክሱ እንዲነሳ ተደርጓል ብለዋል።

“ዛሬ ከቁም እስርነት ይለቀቃል፣ የተመሰረተበት ክስም ይሰረዛል” ብለዋል ባለሥልጣኑ በሰጡት መግለጫ። የእስራቱ ህጋዊነት ላይም የውስጥ ምርመራ ይደረጋል ተብሏል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG