በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በአዲስ አበባ ከታሰሩ ወጣቶች ፍ/ቤት ያልቀረቡ መኖራቸውን ጠበቆች ገለጹ


በአዲስ አበባ ከታሰሩ ወጣቶች ፍርድ ቤት ያልቀረቡ መኖራቸውን ጠበቆች ገለጹ
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:09 0:00

በአዲስ አበባ ከታሰሩ ወጣቶች ፍርድ ቤት ያልቀረቡ መኖራቸውን ጠበቆች ገለጹ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ጉዳይ ከታሰሩ ሰዎች መካከል እስካሁን ፍርድ ቤት ያልቀረቡና በእስር ላይ የሚገኙ መኖራቸውን ጠበቆች ገለጹ።

ከፍርድ ቤት የዋስትና ውሳኔ ውጭ በእስር ላይ የቆዩት ፓስተር ቢኒያም ሽታዬ ደግሞ ትላንት ምሽት ላይ መፈታታቸውን የቤተክርስቲያኗ በጎ ፈቃደኞች የሕግ ቡድን አባል ጠበቃና የሕግ አማካሪ ብሩክ ደረጀ ተናግረዋል፡፡

በሌላ ዜና፣ ከአድዋ ክብረበዓል አከባበር ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር ከዋሉ ግለሰቦች መካከል የሚዲያ ባለሞያ አቤል ገብረኪዳን ከሕግ ውጭ በቁጥጥር ስር መዋሉንና ከአንድ ሳምንት በኋላ ፍርድ ቤት መቅረቡን ጠበቃው አንዱዓለም ቡኬቶ ገልጸዋል፡፡

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እንዲሁም ከአድዋ ክብረ በዓል ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎችን በተመለከተ ያሉ ዝርዝር ጉዳዮችን በቅርቡ ይፋ እንደሚያደርግ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ገልጿል።

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG