በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በአሜሪካ የፕሬዝደንቶች ቀን በመከበር ላይ ነው


ፎቶ ፋይል - በትሪኒዳድ፣ ኮሎራዶ ነዋሪ የሆነው ፊል ቡስቶስ በዋሽንግተን የልደት ቀን በቅናሽ ዋጋ የገዛው ቴሌቪዥን ይዞ በዋሽንግተን ዲሲ፣ እአአ የካቲት 22/1954
ፎቶ ፋይል - በትሪኒዳድ፣ ኮሎራዶ ነዋሪ የሆነው ፊል ቡስቶስ በዋሽንግተን የልደት ቀን በቅናሽ ዋጋ የገዛው ቴሌቪዥን ይዞ በዋሽንግተን ዲሲ፣ እአአ የካቲት 22/1954

በአሜሪካ ዛሬ የፕሬዝደንቶች ቀን ነው። ዕለቱ የመጀመሪያው የአሜሪካ ፕሬዝደንት የልደት ቀን ተደርጎ እንዲከበር በአሜሪካ ም/ቤት ከተደነገጉት 11 በዓላት አንዱ ነው። የፕሬዝደንቶች ቀን ይባል እንጂ፣ ም/ቤቱ ዕለቱን የሰየመው ‘የዋሽንግተን የልደት ቀን’ በሚል ነው።

እንደ ሌሎቹ የአሜሪካ መሥራች አባቶች ሁሉ ጆርጅ ዋሽንግተን በሃገር ደረጃ ክብር እንዲሰጣቸው የሚሹ ዓይነት ሰው እንዳልነበሩ የታሪክ አዋቂዎች ይናገራሉ።

የመንግሥት ሥራ እና ባንኮች ዛሬ ዝግ ናቸው። በመኾኑም በዕለቱ ሰዎች ጊዜ ስለሚኖራቸው ወደ ገበያ የሚያቀኑበት ቀን ስለሆነ የታሪክ አዋቂዎች ቀኑ ትርጉሙ አጥቷል የሚል ቅሬታ ያሰማሉ።

ዋሽንግተን በፕሬዝደንትነት በቆዩባቸው በአብዛኛው ዓመታት አቻዎቻቸው ልደታቸውን ያከብሩላቸው ነበር። ነገር ግን የመጀመሪያው ፕሬዝደንት መሆናቸው ከእንግሊዝ ዘውዳዊ አገዛዝ አንጻር ያለውን ልዩነትና አንድምታ ስለሚያውቁ እንደ ንጉሥ እንዲከበሩ ይፈልጉ እንዳልነበር የታሪክ አዋቂዎች ይናገራሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG