ዋሺንግተን ዲሲ —
የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት አባ ፍራንሲስ የዓለም ሀገራት የኮቪድ-19 የክትባት መድሀኒትን ለሌሎችም እንዲያካፍሉ ጥሪ አድርገዋል። ድንበሮችን የማይለይ ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ በተከሰተበት በአሁኑ ወቅት የብሄርተኝነት ግንቦች መገንባት የለባቸውም ብለዋል።
ሁሉም ሰዎች አስፈላጊውን ህክምናና ክትባት መድሀኒት እንዲያገኙ ዓለም አቀፍ ትብብር እንዲኖር መማጸናቸውን የአሜሪካ ድምጽ ዘጋቢ ሳቢና ካስቴሌፍራኮ ከሮም ዘግባለች።
ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።