በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ለዐስር ቀናት በሆስፒታል የቆዩት አባ ፍራንሲስ ከህመማቸው እያገገሙ መኾኑ ተገለጸ



የሮማ ካቶሊክ ሊቀ ጳጳስ አባ ፍራንሲስ ከሚታከሙበት ጌሜሊ ሆስፒታል ውጭ ሻማ፣ አበባ እና የርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ምስል ተቀምጧል፤ ሮም እአአ የካቲት 24/2025
የሮማ ካቶሊክ ሊቀ ጳጳስ አባ ፍራንሲስ ከሚታከሙበት ጌሜሊ ሆስፒታል ውጭ ሻማ፣ አበባ እና የርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ምስል ተቀምጧል፤ ሮም እአአ የካቲት 24/2025

በሳምባቸው የተፈጠረ ኢንፌክሽን በኩላሊታቸው ላይ ጉዳት ማድረሱን ተከትሎ ላለፉት ዐሥር ቀናት በሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው የቆዩት የሮማ ካቶሊክ ሊቀ ጳጳስ አባ ፍራንሲስ በተሻለ የጤና ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ቫቲካን አስታውቃለች።

"ሌሊቱን በጥሩ ሁኔታ አሳልፈዋል። አባ ፍራንሲስ እንቅልፍ መተኛት እና ማረፍ ችለዋል" ስትል ያስታወቀችው ቫቲካን፣ የ88 ዓመቱ ሊቀ ጳጳስ አሁንም አስጊ ሁኔታ ውስጥ ቢሆኑም አሁን እራሳቸውን ችለው እየተመገቡ መኾኑን እና ምን ዐይነት ሰው ሠራሽ ወይም ፈሳሽ ምግብ እየወሰዱ እንዳልኾነ ተገልጿል። በመልካም ኹኔታ ላይ ይገኛሉም ብሏል።

በሁለቱም ሳምባቸው ላይ ኒሞኒያ የተሰኘ የሳምባ ኢንፌክሽን ያጋጠማቸው አባ ፍራንሲስ ከፍተኛ መጠን ያለው ኦክሲጅን ሲሰጣቸው የቆዩ ሲሆን እሑድ እለት ከህመማቸው አገግመው በቅዳሴ ሥነ ስርዐት ላይ በንቃት መሳተፋቸው ተመልክቷል።

በቫቲካን ሁለተኛ ስፍራ ያላቸው ብፁዕ ካርዲናል ፒዬትሮ ፓሮሊን ትላንት እሑድ ምሽት በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ የተካሄደውን የጸሎት ሥነ ስርዐት መምራታቸውም ተገልጿል።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG