በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አባ ፍራንሲስ የኬንያ ጉብኝታቸውን አጠናቀቁ፤ ዩጋንዳ ገቡ


አቡነ ፍራንሲስ በኬንያ ጉብኝታቸው ወቅት
አቡነ ፍራንሲስ በኬንያ ጉብኝታቸው ወቅት

የሮማው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት አቡነ ፍራንሲስ የናይሮቢ ጉብኝታቸውን ያጠቃለሉት አንድ የተጎሣቆለ አነስተኛ ገቢ ያላቸው ሰዎች መኖሪያ ሠፈር ተመልክተው ነው።

የአባ ፍራንሲስ የኬንያ ጉዞ

please wait

No media source currently available

0:00 0:05:31 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

የሮማው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት አቡነ ፍራንሲስ የናይሮቢ ጉብኝታቸውን ያጠቃለሉት አንድ የተጎሣቆለ አነስተኛ ገቢ ያላቸው ሰዎች መኖሪያ ሠፈር ተመልክተው ነው።

በዚያም ዝቅተኛ ኑሮ በሚኖሩ የከተማይቱ ድሃ ዜጎች ላይ ይፈፀማል ያሉትን “ግፍ” አውግዘዋል።

ለችግሩ ምክንያት ሆነዋል በማለት የከሰሷቸው የሕዝቡን ሃብት አጋብሰው ሥልጣን ላይ የቆዩ “ስግብግቦች” ሲሉ የጠሯቸውን “ጥቂቶች”ን ነው።

አቡነ ፍራንሲስ የኬንያ ጉብኝታቸውን እንዳጠናቀቁ ዛሬ ዩጋንዳ ዋና ከተማ ካምፓላ የገቡ ሲሆን ነገ በዩጋንዳ ሰማዕታት ቤተ መቅደስ ሕዝባዊ የፀሎት ሥነ-ሥርዓት ይመራሉ፡፡

አቡነ ፍራንሲስ በኬንያና በዩጋንዳ በሚያደርጉት ጉብኝት ላይ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሊቀ-ጳጳስ ብፁዕ ወቅዱስ ካርዲናል አቡነ ብርሃነየሱስ ሱራፌል አብረው እየተጓዙ ነው፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

አባ ፍራንሲስ የኬንያ ጉብኝታቸውን አጠናቀቁ
please wait

No media source currently available

0:00 0:01:07 0:00

XS
SM
MD
LG