አዲስ አበባ —
የኢትዮጵያ ሀብት “በብዙ ሀገሮች ተከማችቷል” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ተጠያቂዎቹን ለህግ ለማቅረብ አስተዳደራቸው ከየሀገሩ መንግሥት ጋር እየሠራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ማንነታቸውን በግልፅና በዝርዝር ሳይናገሩ በጥቅሉ “ሌቦች” ሲሉ የጠሯቸው ሰዎች “ያልታወቀባቸው መስሏቸው ሲሸርቡና ሲዶልቱ መዋላቸው ተጨማሪ በሽታ ነው” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
እስካሁን በሙስና ሲጠየቁ የቆዩትም “ቅርንጫፎቹ ብቻ ናቸው” ሲሉ ከመንግሥት ውጭ ባሉ አካላት ሲነሳ የቆየውን ሀሳብ አስተጋብተዋል፡፡
ጠ/ሚኒስትር አብይ አሕመድ ትናንት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የሰጡት ማብራሪያ ትኩረት መሳቡንና ማነጋገሩን ቀጥሏል፡፡
የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ