በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

“ኢትዮጵያን የማሳነስ ልምምድ ለልጆቻችን አናወርስም” ጠ/ሚ ዐብይ አሕመድ

“ኢትዮጵያን የማሳነስ ልምምድ ለልጆቻችን አናወርስም” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ተናገሩ። ኢትዮጵያ የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እንደዚሁም የተለያዩ ሃይማኖቶች አገር መሆኗን ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግሥታቸው ሁሉም ተከባብረው የሚኖሩባት ታላቅ ሃገር ለመገንባት እንደሚሠራም አብራርተዋል።

በደቡብ ክልል ከከፋ ዞን ነዋሪዎች ጋር የተወያዩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአካባቢው እየተነሳ ያለው አዲስ የክልል አደረጃጀት ጥያቄ መመለስ ያለበት ጥልቀት ባለው ውይይትና የጋራ መግባባት መሆኑን አስረድተዋል። አዲስ የክልል አደረጃጀት ጥያቄ በውይይቱ ወቅት ተደጋግሞ ተነስቷል። የቅንጦት ሳይሆን እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ተሳታፊዎች አንስተዋል።

የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

“ኢትዮጵያን የማሳነስ ልምምድ ለልጆቻችን አናወርስም” ጠ/ሚ ዐብይ አሕመድ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:11 0:00


  • 16x9 Image

    እስክንድር ፍሬው

This item is part of

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG