በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኡን ሳን ሱቺ መኖሪያ ቤት ላይ ቦምብ መወርወሩ ተገለፀ


የዲሞክራሲ ታጋይ ኡን ሳን ሱቺ
የዲሞክራሲ ታጋይ ኡን ሳን ሱቺ

ያንኡን ውስጥ በሚገኘው በሚያንማር የቀድሞዋ በርማ የዲሞክራሲ ታጋይ ኡን ሳን ሱቺ መኖሪያ ቤት ላይ ዛሬ ሐሙስ ቦምብ መወርወሩን፣ ቃል አቀባያቸው አስታወቀ፡፡

ያንኡን ውስጥ በሚገኘው በሚያንማር የቀድሞዋ በርማ የዲሞክራሲ ታጋይ ኡን ሳን ሱቺ መኖሪያ ቤት ላይ ዛሬ ሐሙስ ቦምብ መወርወሩን፣ ቃል አቀባያቸው አስታወቀ፡፡

ቃል አቀባዩ ዛወ ሃታይ እንዳስታወቁት፣ ቦምቡ በተወረወረበት ወቅት፣ የኖቤል ሰላም ሎሬቷ ኡን ሳን ሱቺ ቤታቸው አልነበሩም፤ በመኖሪያ ቤቱ ላይም የደረሰ ጉዳት የለም።

ላለፉት ሃያ ዓመታት በቀድሞው የሚያንማር ወታደራዊው ዡንታ የቁም እሥር ላይ የሚገኙት ሳን ሱቺ፤ አብዛኛውን ጊዜ የሚጠፉት፣ አሁን አደጋ በተቃጣበትና ያንኡን ውስጥ በሚገኘው ሐይቅ አካባቢ ባለው መኖሪያቸው ውስጥ እንደሆነ ይታወቃል።

ሳን ሱቺ፣ የበርማ የአሁኗ ሚያንማር የዲሞክረሲ ተምሳሌት ተደርገው ነው፣ በመላው ዓለም የሚታወቁት፡፡

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG