በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የዩናይትድ ስቴትስ የኢሚግሬሽን-ነክ ጉዳዮችና አዲሱ ፕሬዝዳንታዊ ማዘዣ ተከታታይ ውይይት


የሚ ጌታቸው(በስተግራ)፡ ተክለሚካኤል አበበ(መሀል)እና ፍፁም አቻምየለህ(በስተቀኝ)
የሚ ጌታቸው(በስተግራ)፡ ተክለሚካኤል አበበ(መሀል)እና ፍፁም አቻምየለህ(በስተቀኝ)

“በተለያዩ ሁኔታ በፍርድ ቤት ሂደቶች አልፈው ጉዳያቸው ሳይሳካላቸው ቀርቶ ነገር ግን ወንጀል ስለሌላቸው ሊሆን ይችላል ከአገር ያልተባረሩ፤ በዓመት ወይ በስድስት ወር አንዴ ወደ ኢሚግራሽን መሥሪያ ቤት እየፈረሙ በሰላም የመሚኖሩ .. ለእነኚህና ለሌሎች አሁን አሳሳቢ ሁኔታ እየተፈጠረ ነው።” የሚ ጌታቸው በካሊፎኒያ የአሜሪካ የሕግ-ጠበቆች ማኅበር የሳንታክላራ ቫሊ ሊቀመንበር።

የዩናይትድ ስቴትስ የኢሚግሬሽን-ነክ ጉዳዮችና አዲሱ ፕሬዝዳንታዊ ማዘዣ
please wait

No media source currently available

0:00 0:20:28 0:00
የውይይቱን ሁለተኛ ክፍል ከዚህ ያድምጡ።
please wait

No media source currently available

0:00 0:15:48 0:00
የውይይቱን ሦሥተኛና የመጨረሻ ክፍል ከዚህ ያድምጡ።
please wait

No media source currently available

0:00 0:09:40 0:00

በብዙ ሚልዮን የሚቆጠሩ በዩናይትድ ስቴትስ የሚኖሩ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸውንና ሌሎችን ያሳሰበ ርዕሰ ጉዳይ ነው።

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባሳለፍነው ሳምንት መገባደጂያ ያወጡትን አዲሱን ፕሬዝዳንታዊ ማዘዣ ጨምሮ በዩናይትድ ስቴትስ የኢሚግሬሽን ፖሊሲ ዙሪያ እየመጡ ያሉና “ይመጡ ይሆናል” የተባሉ ለውጦችና አንድምታ በጥልቀትና በቅርበት ለማየት የሚጥር ከሕግ ባለሞያዎች ጋር የተካሄደ ውይይት ነው።

ተወያዮች:- የሚ ጌታቸው በካሊፎኒያ ክፍለ ግዛት በሳንሆዜ የአሜሪካ የሕግ-ጠበቆች ማኅበር የሳንታክላራ ቫሊ ሊቀመንበር ናቸው። በስደተኞች ጉዳይ ተሟጋችነትም ይታወቃሉ።

አቶ ፍጹም አቻምየለህ በዋሽንግተን ዲሲና ቨርጂኒያ በጥብቅና ሥራ የተሰማሩና በስደተኞች ሕግ ዙሪያ ለረዥም ጊዜ ያገለገሉ ናቸው።

አቶ ተክለሚካኤል አበበ ደግሞ በካናዳ ቶሮንቶ በጥብቅና ሥራ የተሰማሩ ናቸው። የውይይቱን የመጀመሪያ ክፍል ከዚህ ያድምጡ።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG