ዋሺንግተን ዲሲ —
የሦስቱን ሀገሮች ተወካዮች ስብሰባን የሚያስተናግዱት የዩናይትድ ስቴትስ የገንዘብ ሚኒስትር ሲሆኑ የኅዳሴ ግድብ የውሀ ሙሌትን በሚመለከት ሥምምነት ላይ ለመድረስ እየጣሩ ናቸው።
በኢትዮጵያና በግብጽ መካከል “የውሀ ጦርነት” ሊያስነሳ ይችላል የሚል ስጋት እንዳለ ተዘግቧል።
ስብሰባው ማክሰኞና ረዕቡ እንዲካሄድ ነበር የታቀደው፤ ነገር ግን እስከ ዛሬ መቀጠሉ አልቀረም።