በመጋቢት 1/2010 በሞያሌ ግድያ ፈፀመዉ በቁጥጥር ያሉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት እስካሁን ለፍርድ አለመቅረባቸውን የሞያሌ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። ሁለት የግድያው የዐይን ምስክሮች ግድያው እንደደረሰ ቃላቸዉን ለመንግሥት ሰጥተው “ለምስክርነት ትጠራላችሁ” ቢባሉም እስካሁን ግን ማንም እንዳልጠየቃቸው ለአሜርካ ድምፅ ተናግረዋል።
የሞያሌ ወረዳ ፍትህ ቢሮ በበኩሉ ግድያዉን የፈፀሙ ለችሎት ለማቅረብ ከኦሮሚያ ክልል ኃላፊዎችና ከሀገር መከላከያ ሚኒስቴር ጋር እየሰራ መሆኑን ነው የገለፀው።
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ