በጦርነትና ግጭት ውስጥ ሆነው የተፈተኑና ወደ መንግሥት ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ያላመጡ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከ2014 ዓ.ም መደበኛ ተፈታኞች ጋር እንዲፈተኑ ተወሰነ። የትምህርት ሚኒስቴር ከክልል እና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች ጋር በመሆን ዛሬ ለመንግሥት መገናኛ ብዙኃን በሰጠው መግለጫ፣ ከዚህ በፊት በተወሰነው የመቁረጫ ነጥብ ወደ ዩኒቨርሲቲ ከሚገቡት ተማሪዎች ውጭ ግጭት አለባቸው ከተባሉ ክልሎች ተጨማሪ ተማሪዎች እንደሚገቡ አስታውቋል፡፡ ጉዳዩን ሲከታተል የነበረው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ እንዲሁም የሕዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም የሚኒስቴሩን እርምጃ አድንቀዋል።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ፌብሩወሪ 08, 2023
ንግድ ባንክ በትግራይ እንደገና አገልግሎት መስጠት ጀመረ
-
ፌብሩወሪ 07, 2023
ጆ ባይደን ዓመታዊ ንግግራቸውን ዛሬ ያደርጋሉ
-
ፌብሩወሪ 07, 2023
አቡነ ፍራንሲስ በደቡብ ሱዳን ሰላም እንዲሰፍ ተማፀኑ
-
ፌብሩወሪ 07, 2023
ወደ ትግራይ ክልል የሚወስዱ መንገዶች ጥገና መጠናቀቁ ተገለፀ
-
ፌብሩወሪ 07, 2023
የደቡብ ክልል ውሳኔ ሕዝብ ውጤት እየተለጠፈ ነው
-
ፌብሩወሪ 07, 2023
- የልብ ጤና ጉዳይ በዩናይትድ ስቴትስ ቁጥር አንድ ገዳዩ የልብ ደም ስሮች በሽታ