በጦርነትና ግጭት ውስጥ ሆነው የተፈተኑና ወደ መንግሥት ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ያላመጡ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከ2014 ዓ.ም መደበኛ ተፈታኞች ጋር እንዲፈተኑ ተወሰነ። የትምህርት ሚኒስቴር ከክልል እና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች ጋር በመሆን ዛሬ ለመንግሥት መገናኛ ብዙኃን በሰጠው መግለጫ፣ ከዚህ በፊት በተወሰነው የመቁረጫ ነጥብ ወደ ዩኒቨርሲቲ ከሚገቡት ተማሪዎች ውጭ ግጭት አለባቸው ከተባሉ ክልሎች ተጨማሪ ተማሪዎች እንደሚገቡ አስታውቋል፡፡ ጉዳዩን ሲከታተል የነበረው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ እንዲሁም የሕዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም የሚኒስቴሩን እርምጃ አድንቀዋል።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ማርች 14, 2025
በአፍሪካ የኅይል አቅርቦት ላይ ያተኮረውና በዋሽንግተን ዲሲ የተካሔደው ጉባኤ
-
ማርች 14, 2025
የኢትዮጵያውያት ሴቶች ጥያቄ ምንድን ነው? - የአድማጭ ተመልካቾች አስተያየት
-
ማርች 13, 2025
አርቲስት አንዱዓለም ጎሣ ተጨማሪ 13 ቀናትን በእስር እንዲቆይ ፍርድ ቤት ፈቀደ
-
ማርች 13, 2025
ሩሲያ የተቆጣጠረቻቸውን የዩክሬን ግዛቶች እንደያዘች መቀጠል ትሻለች