በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰላም መጠናቀቁን መንግሥት አስታወቀ


የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት  ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ተፈራ ፈይሳ
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት  ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ተፈራ ፈይሳ

ፈተናው ለተማሪዎች ከመሰጠቱ በፊት ተሰርቆ ስለመውጣቱ በማኅበራዊ ሚዲያዎች የተለቀቁ መረጃዎች የሚያሳዩ ሲሆን መንግሥትም ከተለያዩ አካላት መረጃዎች እንደደረሱት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ተፈራ ፈይሳ ገልጸዋል፡፡

ጉዳዩን በማጣራት እርምጃ እንደሚወስድም አቶ ተፈራ ገልፀዋል፡፡ አሁን ላይ ፈተናውን የተፈተኑ ተማሪዎች የውጤት ምዘናና የዩኒቨርሲቲ ምደባ፣ በጸጥታ ምክንያት ያልተፈተኑ ቀሪ ተማሪዎች ከተፈተኑ በኋላ በጋራ እንደሚገለጽም ምክትል ዳይሬክተሩ አመልክተዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡

የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰላም መጠናቀቁን መንግሥት አስታወቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:06 0:00



XS
SM
MD
LG