በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የትግራይ መንግሥት ሳያውቀው መቀሌ የገቡ የፀረ ሽብር የፌደራል ፖሊስ አባላት


አሉላ አባነጋ ኤርፖርት
አሉላ አባነጋ ኤርፖርት

ከ18 ቀናት በፊት የትግራይ ክልል መንግሥት ሳያውቀው ወደ መቀሌ ከተማ ገብተው የነበሩ 45 የፀረ ሽብር የፌደራል ፖሊስ አባላት ወደ መጡብት በዛሬው ዕለት ከተያዙበት ተለቀው ወደ አዲስ አበባ ተመልሰዋል።

ከ18 ቀናት በፊት የትግራይ ክልል መንግሥት ሳያውቀው ወደ መቀሌ ከተማ ገብተው የነበሩ 45 የፀረ ሽብር የፌደራል ፖሊስ አባላት ወደ መጡብት በዛሬው ዕለት ከተያዙበት ተለቀው ወደ አዲስ አበባ ተመልሰዋል።

እነዚህ አባላት መቀሌ ከተማ እንደገቡና በአሉላ አባነጋ ኤርፖርት አካባቢ የሚገኝ የፌደራል ፖሊስ ካምፕ በትግራይ ክልል የፀጥታ ኃይል ሥር እንዲቆዩ ተደርጓል ተብሏል።

የክልሉ የህዝብ ግንኙነት ቢሮ ኃላፊ አቶ ረደኢ ሐለፎም አባላቶቹ ወደ ትግራይ የመጡበት አካሄድ ሥህተት ነበረበት እኛ ሳናውቀው ነው የገቡት አሁን ግን ከፌደራል መንግሥትጋ በመረዳዳት ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደርጓል ብለዋል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ

የትግራይ መንግሥት ሳያውቀው መቀሌ የገቡ የፀረ ሽብር የፌደራል ፖሊስ አባላት
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:17 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG