በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

 
የመቐለ ኤፍ ኤም ራድዮ ጣቢያን ለመቆጣጠር ሞክረዋል የተባሉ ክስ እንደቀረበባቸው ተገለጸ

የመቐለ ኤፍ ኤም ራድዮ ጣቢያን ለመቆጣጠር ሞክረዋል የተባሉ ክስ እንደቀረበባቸው ተገለጸ


በመቐለ የሚገኘው ኤፍኤም 104.4 ራዲዮ ጣቢያ / ቪኦኤ
በመቐለ የሚገኘው ኤፍኤም 104.4 ራዲዮ ጣቢያ / ቪኦኤ

ትላንት ረቡዕ ጥር 21 ቀን 2017 ዓ.ም በዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረሚካኤል ቡድን የተሾሙ ግለሰብ በትግራይ ክልል የመቐለ ኤፍ ኤም ራድዮ ጣቢያን ለመቆጣጠር መሞከራቸውን የጣቢያው ጊዜያዊ ሥራ አስከያጅ ገለጹ። ድርጊቱን ፈጽመዋል የተባሉ ግለሰብ ላይም ጣቢያው ክስ መመስረቱን ተናገሩ።

ጣቢያውን ሊቆጣጠሩ ነበር በሚል ወቀሳ ከቀረበባቸው ፣ አቶ ዘመንፈስቅዱስ ፍስሃ ምላሽ ለማግኘት በእጅ ስልካቸው ላይ በተደጋጋሚ ደውለን ስብሰባ ላይ መሆናቸው ስለገለፁን ምላሻቸውን ማካተት አልቻልንም።

የመቐለ ኤፍ ኤም ራድዮ ጣቢያን ለመቆጣጠር ሞክረዋል የተባሉ ክስ እንደቀረበባቸው ተገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:14 0:00

ጉዳዩ ኣስመልክቶ ከመቐለ ፖሊስ አዘዥ ኮማንደር አንድነት ነገሰ ተጨማሪ ማብራርያ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም። ሆኖም የመቐለ ከተማ ፖሊስ መምርያ በፌስቡክ ገጹ በአወጣው መረጃ፣ ትላንት ረቡዕ ጥር 21 ቀን 2017 ዓ/ም በመቐለ ኤፍኤም 104.4 “የተሾመኩት እኔ ነኝ” በሚል የተነሳ፣ ጊዜያዊ አለመግባባት ተፈጥሮ እንደነበርና ፖሊሰ ሁኔታው ለማረጋጋት በቦታው ተገኝቶ እንደነበር አስታውቋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG