በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የብሪታንያ ጠ/ሚ ከፓርቲ መሪነታቸው ይለቃሉ


የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ተሬሳ ሜይ
የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ተሬሳ ሜይ

የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ተሬሳ ሜይ ከወግ አጥባቂ ፓርቲው መሪነታቸው በዛሬው ዕለት ይለቃሉ። ተተኪያቸው የሚመረጡበት የመጀመሪያ ዙር ምርጫ በመጪው ሳምንት ይጀመራል ተብሎ ይጠበቃል።

ሜይ ፓርቲያቸው እዲስ መሪ እስኪመርጥ ምናልባትም እስከመጪው የአውሮፓውያን ሃምሌ ወር ድርስ በፓርቲው መሪነት ይቆዩ ይሆናል። ነገር ግን ሃገራቸው ከአውሮፓ ህብረት ለሚመጣው ጥቅምት መጨረሻ የጊዜ ሰሌዳ የተያዘለት ዕቅድ የመምራት ኃላፊነታቸውን አስረክበዋል።

ተሬሳ ሜይን የሚተኳቸው አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር በሳቸው ዕቅድ ላይ ነፍስ ዘርተውበት የአወጣጥዋን ዕቅድ እንደገና እንዲዘገይ ሊሞክሩም ሆነ ያለአንዳች ሥምምነት ከህብረቱ ለመውጣት ለመወሰን የአምስት ወር ጊዜ ይኖራቸዋል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG