በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ናጂብ ራዛክ በብዙ ቢልዮን ዶላር ቅሌት ውስጥ አሉበት በሚል ክስ ተያዙ


የማሌዥያ ጠ/ሚኒስትር የነበሩት ናጂብ ራዛክ
የማሌዥያ ጠ/ሚኒስትር የነበሩት ናጂብ ራዛክ

የማሌዥያ ጠ/ሚኒስትር የነበሩት ናጂብ ራዛክ ብዙ ቢልዮን ዶላርን በሚያካትት ቅሌት ውስጥ አሉበት በሚል ክስ ተይዘዋል።

ናጂብ ዛሬ በሀገሪቱ ፀረ ሙስና ኮሚሽን ኃይሎች አቤታቸው እንዳሉ መያዛቸው ታውቋል። የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር የተያዙት ሲአርሲ ኢንተርናሽናልና /IMDB/ በተባሉት ተቋማት ላይ ከሚደረገው ምርመራ ጋር በተያይዘ ነው ተብሏል።

ናጂብ ራዛክ ነገ በኦፊሴል ክስ ይቀርብባቸዋል። /IMDB/ ሥልጣን ላይ እንዳሉ የከፈቱት ሲሆን $4.5 ቢልዮን ዶላር ከተቋሙ ተዘርፏል ይላል የዩናይትድ ስቴትስ የፍርድ ሚኒስቴር። ከተዘረፈው ገንዘብ የተወሰነው በናጂብ የግል ባንክ ሂሳብ ገብቷል የሚል ነው ክሱ።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG