በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሰማያዊ ፓርቲ መሪዎችና ቀስቃሾች ባሕር ዳር ላይ ታሠሩ


Ethiopian Blue party Logo
Ethiopian Blue party Logo

የሰማያዊ ፓርቲ የብሄራዊ ምክር ቤት አባላትና ቀስቃሾች ለሕገወጥ ስብሰባ ቀስቅሳችኋል ተብለው በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ ነገሠ ተፈረደኝ ለቪኦኤ አስታወቁ፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ መሪዎችና ቀስቃሾች ባሕር ዳር ላይ ታሠሩ
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:28 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

የሰማያዊ ፓርቲ የብሄራዊ ምክር ቤት አባላትና ቀስቃሾች ለሕገወጥ ስብሰባ ቀስቅሳችኋል ተብለው በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ ነገሠ ተፈረደኝ ለቪኦኤ አስታወቁ፡፡

ፓርቲው ለነገ፤ ዕሁድ ሰኔ 26/2008 ዓ.ም ባሕር ዳር ከተማ ውስጥ ለማካሄድ አቅዶት ለነበረው ስብሰባ ከአስተዳደሩ ፍቃድ ማግኘታቸውን አቶ ነገሠ ገልፀዋል፡፡

ይሁን እንጂ ፖሊስ ሁለት የከተማው ነዋሪዎች የሆኑ የፓርቲውን ደጋፊዎች ጨምሮ ለስብሰባው ከአዲስ አበባ ወደ ባሕርዳር የተጓዙ የፓርቲው የብሄራዊ ምክር ቤት አባላትን በጠቅላላው አሥር ሰዎችን ማሠሩን ምክትል ሊቀመንበሩ አክለው ጠቁመዋል፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ መሪዎችና ደጋፊዎቹ የታሠሩት ባሕር ዳር ከተማ ውስጥ ነው፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

XS
SM
MD
LG