በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በጎንደር ከተማ ትላንት በነበረው የተኩስ ልውውጥ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ ሦስት ሰዎች መቁሰላቸው ተነገረ


ፎቶ ፋይል፦ ጎንደር
ፎቶ ፋይል፦ ጎንደር
በጎንደር ከተማ ትላንት በነበረው የተኩስ ልውውጥ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ ሦስት ሰዎች መቁሰላቸው ተነገረ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:01 0:00

በታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ ትላንት ደርሷል በተባለው የተኩስ ልውውጥ በሁለት ቤተ እምነቶች ላይ በደረሰው ጥቃት 2 ሰዎች ሲሞቱ 3 ሰዎች መቁሰላቸውን በኢትዮጵያ የኦርቶዶህ ተዋህዶ የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ተናገሩ፡፡

ዋና ሥራ አስኪያጁ ሊቀ ህሩይ አባ ዮሴፍ ደስታ ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት በከተማው ዙሪያ እና በከተማው ውስጥ በሚገኙ አማንኤል እና ፈለገህይወት ቤዛዊት ማርያም በተባሉ ቤተ ክርስቲያኖች አንድ አገልጋይና አንድ ተማሪ መሞታቸውን ተናግረዋል፡፡

የፈለገ ህይወትቤዛዊት ማሪያም አስተዳዳሪ መሆናቸውን የነገሩን መልዓከ ህይወት መምህር ዐቢይ ዘላለም እንደተናገሩት በቤተክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ ውስጥ ያልታወቁ የታጠቁ ኃይሎች ገብተው አንድ አገልጋይ ተኩሰው መግደላቸው እና ሌላ አብሮት የነበረ ተማሪን ማቁሰላቸውን ነግረውናል፡፡

የጎንደር ከተማ አስተዳደር ዛሬ ከሰዓት በፌስ ቡክ ገፁ ባወጣው መረጃ በትናንትናው ዕለት መስከረም 7/2017 ዓ/ም በፀጥታ ችግር ምክንያት ተቋርጦ የነበረዉ የትራንስፖርት አገልገሎት እና የንግድ ተቋማት አገልግሎት ዛሬ መስከረም 8/2017 ዓ.ም በከተማው በሁሉም አካባቢዎች በተሟላ ሁኔታ መጀመሩን ገልፆል፡፡ ስጋት ገብቶናል ያሉ ነዋሪዎች ግን አሁንም ከቤት መውጣት አለመቻላቸውን ተናግረዋል፡፡

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG