ዋሺንግተን ዲሲ —
የደቡብ ኮሪያ የክረምት ኦሎምፒክስ አስተናጋጆች፣ ከፕዮንግያንግ በስተሰሜን የሚገኘውንና ከፍተኛ ወታደራዊ ቀጣና የሚገኝበትን ድንበር፣ ከመላው ኮሪያ ሰላም አንፃር ወደ ቱሪስት መስህብነት ለመቀየር እየሰሩ መሆናቸው ተገለፀ።
ሰሜን ኮሪያ በዚህ በመጪው ኦሎምፒክስ ውድድር መሳተፏ፣ በአካባቢው የነበረውን ውጥረት ይልቁንም፣ የሰሜን ኮሪያን የኑክሊየር ጦር መሣሪያ ፕሮግራም ወደ ማርገቡም ተመልክቷል።
በደቡብ ኮሪያዋ ‘PyeongChang’ የሚከናወነው የዘንድሮው የ2018 ኦሎምፒክ፣ ለአፍታም ቢሆን የደቡብና ሰሜን ኰሪያን አንድነት ያመጣ መንፈስ እንደፈጠረ ነዋሪዎች ይናገራሉ።
ለውድድሩ፣ ከ45 በላይ የደቡብ ኮሪያ ባሕላዊ ክንውኖች እንደሚዘጋጁና እነዚህም በሁለቱ ኮሪያዎች አንድነት ላይ ያተኮሩ እንደሚሆኑ ታውቋል።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ