በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኮምበልቻ መጋዘን እንደገና ዝግጁ ነው


የኮምበልቻ መጋዘን
የኮምበልቻ መጋዘን

መንግሥት "ከ500 ሺህ ኲንታል በላይ የእርዳታ እህል በህወሓት ታጣቂዎች ተዘርፎበታል" ያለው የኮምበልቻ መጋዘን ለቀጣይ አገልግሎት መዘጋጀቱን ገለፀ።

ህወሓት ውንጀላውን አስተባብሏል።

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኙ ተፈናቃዮች በቂ ድጋፍ እየቀረበላቸው አለመሆኑን የገለፁ ሲሆን ዋነኛው ምክንያት የመጋዘኑ መዘረፍ መሆኑን የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደበበ ዘውዴ ተናግረዋል።

መንግሥት በቀጣይነት በጦርነቱ ምክንያት ለችግር የተጋለጡ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ለመደገፍ ከፍተኛ መጠን ያለው እህል ከውጭ በማስገባት ላይ እንደሆነ፣ የኮምበልቻው መጋዘንም ለአገልግሎት መዘጋጀቱንም ጠቁመዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ።

የኮምበልቻ መጋዘን
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:37 0:00


XS
SM
MD
LG