ኮምቦልቻ —
የኢትዮጵያ መንግሥት በአሸባሪነት የፈረጀውና ራሳቸውን የትግራይ ሠራዊት ብለው የሚጠሩት የህወሓት ታጣቂዎች ኮምቦልቻ ከተማን ተቆጣጥረው በነበሩትበት ከጥቅምት 21 እስከ ኅዳር 27/2014 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የኮምቦልቻ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት መጋዘኖች ተሰብረው ከ100 ሺሕ ኩንታል በላይ የእርዳታ አህል መዘረፉን ኮሚሽኑ አስታወቀ።
የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት መጥፎ አሻራ ካሳረፈባቸው ከተሞች አንዱ ወደ ሆነው ደሴ ከተማ ተጉዞ ሰሞኑን ቆይታውን ሲያካፍለን የነበረው ዘጋቢያችን ኬኔዲ አባተ ዛሬ ደግሞ ኮምቦልቻ ከተማ ይገኛል።
ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።