ዋሽንግተን ዲሲ —
አራት ኢትዮጵያውያን በአሜሪካ ታዋቂ የቴሌቭዥን ፕሮግራም ላይ በጋራ ባሳዩት የሰርከስ ትርዒት በሁለት ቀናት ውስጥ በተመልካች ብዛት ቀዳሚውን ስፍራ ይዘዋል።
ከአሜሪካ የቴሌቭዥን ጣቢያ NBC ጋራ በመተባበር “Little Big Shots” የተሰኘውን ፕሮግራም የሚሠሩት ሁለቱ ታዋቂ አሜሪካውያን ስቲቭ ሃርቬይና ኤለን ዲጀነረስ ናቸው።
በዚህ ፕሮግራም ላይ የፕሮግራሙ አቅራቢ ስቲቭ ከትላንት በስቲያ “ኪሪኩ ብራዘርስ” በሚል የቡድን መጠሪያ የሚታወቁ ሁለት ታዳጊዎችና ሁለቱ ወጣቶችን አቅርቦ ተመልካቹን አስደንቋል።
ለመሆኑ እነዚህ ታዳጊና ወጣቶች እነማን ናቸው? በዚህ ፕሮግራም ላይስ እንዴት ተገኙ?
ጽዮን ግርማ “ኪሪኩ ብራዘርስ” አባላትና ቤተሰቦቻቸውን አነጋግራ ተከታዩን ዘግባለች።
(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ)
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ