በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በሃይቲ ከተደራጁ ወንጀለኞች ጋራ በተፈጠረ ግጭት አንድ የኬንያ ፖሊስ ተገደለ


የሕግ አስከባሪ አባላት በሲቪሎች፣ በብሔራዊ ፖሊስ አባላት እና በተደራጁ ወንጀለኞች መካከል ግጭት ከተከሰተ በኋላ አካባቢው በመድረስ አካባቢውን ጠብቀዋል እአአ የካቲት 23/2025
የሕግ አስከባሪ አባላት በሲቪሎች፣ በብሔራዊ ፖሊስ አባላት እና በተደራጁ ወንጀለኞች መካከል ግጭት ከተከሰተ በኋላ አካባቢው በመድረስ አካባቢውን ጠብቀዋል እአአ የካቲት 23/2025

በኬንያ የሚመራው የጸጥታ ተልዕኮ ኃይል ከሰኔ ወር ጀምሮ በሃይቲ ከተሰማራ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ እሑድ ዕለት፣ ከዋና ከተማው ፖርት-ኦው-ፕሪንስ በስተሰሜን በሚገኝ ስፍራ አንድ የኬንያ ፖሊስ መገደሉን የተልዕኮው ባለሥልጣናት አስታወቁ።

ከተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ የፀጥታ አባላትን ያካተተው የሄይቲ የድጋፍ ተልዕኮ እሑድ እለት ባወጣው መግለጫ ኬንያዊው የፖሊስ አባል ከወንበዴዎቹ ጋራ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ላይ መቁሰሉ እና ወደ ሆስፒታል መወሰዱን፣ በኋላም ህይወቱ ማለፉን አመልክቷል።

የተልዕኮው ቃል አቀባይ ጃክ ኦምባካ ለሮይተርስ በሰጡት ቃል፣ እሁድ እለት የደረሰው ጉዳት፣ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሚደገፈው የፀረ-ወንበዴ ኃይል ወደ ሄይቲ ከገባ ወዲህ የመጀመሪያው ነው።

"ህይወቱ ላለፈው ጀግናችን ክብር እንሰጣለን" ያለው መግለጫው "እነዚህን ወንበዴዎች እስከመጨረሻው ድረስ እንሳድዳቸዋለን። አናሳፍርህም" ሲል መልዕክት አስተላልፏል።

የኬንያው ፖሊስ ህይወት ያለፈው፣ ባለፉት ሳምንታት በሃይቲ ዋና ከተማ ፖርት-ኦው-ፕሪንስ አካባቢ በተደራጁ ወንጀለኞች የሚደርሱ ሁከቶች እየጨመሩ ባሉበት ወቅት ነው።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG