በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኬንያ ሙስሊሞች ክርስቲያኖችን ከአል ሻባብ ጥቃት ሸፈኑ


ፎቶ - ፋይ፤ አል ሻባብ ቀደም ሲል ማንዴራ ውስጥ አድርሶት ከነበረ ጥቃት
ፎቶ - ፋይ፤ አል ሻባብ ቀደም ሲል ማንዴራ ውስጥ አድርሶት ከነበረ ጥቃት

የአልሸባብ ደጋፊዎች እንደሆኑ የሚታመን ጠብመንጃ አንጋቢዎች ባለፈው ሰኞ ከማንዴራ ወደ ናይሮቢ ያመራ የነበር የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ማገታቸው ሙስሊም እና ክርስቲያን ተሣፋሪዎችን ለመለያየት ጥረት ማድረጋቸው ተዘግቧል።

please wait

No media source currently available

0:00 0:03:44 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

የአልሸባብ ደጋፊዎች እንደሆኑ የሚታመን ጠብመንጃ አንጋቢዎች ባለፈው ሰኞ ከማንዴራ ወደ ናይሮቢ ያመራ የነበር የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ማገታቸው ሙስሊም እና ክርስቲያን ተሣፋሪዎችን ለመለያየት ጥረት ማድረጋቸው ተዘግቧል።

ሙስሞቹ መንገደኞች ግን የጥቃት አድራሾቹን ትዕዛዝ አንቀበልም ብለው ክርስቲያኖቹ ለመለየት ፈቃደኛ እንዳልሆኑ ተዘግቧል፡፡

ከገደላችሁ ሁላችንንም ግደሉ ብለው አብረው ቆመዋል፡፡

ሙስሊሞቹ ሂጃብና ጥምጥሞቻቸውን ለክርስቲያኖቹ እየሰጡ ከጥቃት ለመከላከል ሞክረዋል፡፡

የናይሮቢ ነዋሪዎች ይህንን ኬንያዊያኑ ሙስሊሞች ማንዴራ አውራጃ ውስጥ የፈፀሙትን የፈፀሙትን ተግባር የጀግንነትና ኬንያዊ ምግባር ሲሉ አወድሰውታል፡፡

አል ሻባብ ባለፈውም ዓመት እዚያው ማንዴራ ውስጥ እንዲሁ አንድ የመንገደኞች አውቶቡስ ላይ ድንገተኛ አደጋ ጥለው ሙስሊም ያልሆኑ 28 ተሣፋሪዎችን ለይተው ካወጡ በኋላ ገድለዋቸዋል፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

XS
SM
MD
LG