በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በኬንያ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በፖሊሶችና በተቃዋሚዎች መካከል ግጭት ተፈጠረ


ኬንያ ውስጥ ዛሬ የተካሄደው የፕሬዚዳንታዊ ማጣርያ ምርጫ በፖሊሶችና በተቃዋሚዎች መካከል ግጭት አስከትሏል። ተቃዋሚዎች በሚበዙባቸው አካባቢዎች ደግሞ የምርጫ ጣብያዎች ሳይከፈቱ ቀርተዋል።

ኬንያ ውስጥ ዛሬ የተካሄደው የፕሬዚዳንታዊ ማጣርያ ምርጫ በፖሊሶችና በተቃዋሚዎች መካከል ግጭት አስከትሏል። ተቃዋሚዎች በሚበዙባቸው አካባቢዎች ደግሞ የምርጫ ጣብያዎች ሳይከፈቱ ቀርተዋል።

የምርጫ ኮሚሽን ኃላፊ ዋፉላ ቼቡካቲ በምዕራብ ኬንያ ተቃውሚዎች በሚበረቱባቸው አራት ወረዳዎች ላይ በፀጥታ ተግዳሮቶች ምክንያት ምርጫው እስከ መጪው ቅዳሜ ድረስ እንዲዘገይ መደረጉን አስታውቀዋል።

በኬንያ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በፖሊሶችና በተቃዋሚዎች መካከል ግጭት ተፈጠረ
please wait

No media source currently available

0:00 0:00:42 0:00

ኪሱሙ ላይ በፖሊሶችና በተቃዋሚዎች መካከል በተነሳ ግጭት አንድ ሰው በተኩስ መገደሉን ፖሊሶች ገልፀዋል። በርካታ የኪሱሙ የምርጫ ጣብያዎች ተዘግተዋል። የምርጫ ባለሥልጣኖችም ሊገኙ አልቻሉም።

ናይሮቢ በሚገኘው ደሳሳ ሰፈር ኪቤራ ተቃዋሚዎች በምርጫ ጣብያው ፊት መሰናክል ለመሥራት ሲሞክሩ ፖሊሶች ዕምባ አስመጪ ጋዝ ተኩሰውባቸዋል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG