በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኦሮምያ አንድነትና ነፃነት ግንባር ደርጅት ልዑክ በአዲስ አበባ

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አሕመድ በውጭ ሀገር ላሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያቀረቡትን ጥሪ መሰረት በማድረግ የኦሮምያ አንድነት እና ነፃነት ግንባር የተባለው ደርጅት ልዑክ ዛሬ አዲስ አበባ እንደሚገባ ተዘግቧል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አሕመድ በውጭ ሀገር ላሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያቀረቡትን ጥሪ መሰረት በማድረግ የኦሮምያ አንድነት እና ነፃነት ግንባር የተባለው ደርጅት ልዑክ ዛሬ አዲስ አበባ እንደሚገባ ተዘግቧል።

የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ኃላፊ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፁት፥ የኦሮምያ አንድነት እና ነፃነት ግንባር ልዑክ የድርጅቱ አመራር በሆኑት በብርጋዴር ጀነራል ከማል ገልቹ መሪነት ዛሬ አዲስ አበባ እንደሚገባ ይጠበቃል።

የኦሮምያ አንድነት እና ነፃነት ግንባር አገር የሚገባው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ በውጭ ሀገር ላሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ ሀገር ገብተው በሰላማዊ መንገድ እንዲንቀሳቀሱ፣ በሀገር ግንባታ ሂደቱም በጋራ እንዲሰሩ በተደጋጋሚ ያደረጉትን ጥሪ መሰረት በማድረግ ነው።

This item is part of

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG