በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

እስራኤል ደቡብ ሊባኖስን ደበደበች


ፎቶ ፋይል፦ የእስራኤል አምባሳደር ጊላድ ኤርዳን
ፎቶ ፋይል፦ የእስራኤል አምባሳደር ጊላድ ኤርዳን

የጸጥታው ምክር ቤት ሐማስን እንዲያወግዝ የእስራኤል አምባሳደር ጠየቁ

ታጣቂዎች፥ በድንበር በኩል ሰርገው ገብተዋል፤ በሚል፣ እስራኤል፣ ዛሬ ሰኞ፣ የደቡብ ሊባኖስ የድንበር አካባቢን በከባድ መሣሪያ ደብድባለች፡፡

በሊባኖስ የሚገኘውና በኢራን የሚደገፈው ሔዝቦላህ በበኩሉ፣ ድንበር ጥሶ ገብቷል፤ የሚለውን ክስ አስተባብሏል። ከእስራኤል ጋራ ግጭት አለ፤ የሚለውንም አጣጥሏል።

የሐማስ የጦር ወንጀል በማያሻማ መንገድ ሊወገዝ ይገባል፤”

ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የእስራኤል አምባሳደር፣ የጸጥታው ም/ቤት ሐማስን እንዲያወግዝ ጠይቀዋል።

“የሐማስ የጦር ወንጀል በማያሻማ መንገድ ሊወገዝ ይገባል፤” ሲሉ ተደምጠዋል አምባሳደሩ ጊላድ ኤርዳን።

የጸጥታው ም/ቤት፣ ትላንት ምሽት ዝግ ስብሰባውን ከማድረጉ በፊት፣ ለጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት አምባሳደሩ፣ “እስራኤል አፋጣኝ ድጋፍ ሊሰጣት ይገባል፤” ሲሉም አክለዋል።

አምባሳደሩ የሐማስን የቅዳሜ ድንገተኛ ጥቃት፣ እ.አ.አ በ2001 አል ቃዒዳ በአሜሪካ ምድር ላይ ከፈጸመውና ሦስት ሺሕ የሚጠጋ ሕይወትን ከቀጠፈው ጥቃት ጋራ አመሳስለውታል።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG