በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

እስራኤል በራፋ የምታካሂደውን ጥቃት እንድታቆም ደቡብ አፍሪካ ለዓለሙ ችሎት ላቀረበችው ጥሪ ምላሽ ሰጠች


በኔዘርላንድስ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ቩሲሙዚ ማዶንሴላ
በኔዘርላንድስ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ቩሲሙዚ ማዶንሴላ

እስራኤል ደቡባዊ ጋዛ በምትገኘው ራፋ ላይ የከፈተችውን ጥቃት አስመልክቶ ‘ተጨማሪ የአስቸኳይ ጊዜ እርምጃዎችን እንዲወሰዱ’ ስትል ደቡብ አፍሪካ ለአለም አቀፉ የወንጀል ችሎት ያቀረበችውን ጥያቄ በመቃወም ተከራክራለች።

በኔዘርላንድስ የደቡብ አፍሪቃው አምባሳደር ቩሲሙዚ ማዶንሴላ ትላንት ሐሙስ ለዓለም አቀፉ ችሎት ዳኞች ባቀረቡት ጥያቄ እስራኤል “ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ እና በአፋጣኝ፣ ሙሉ በሙሉ ጦሯን ከመላው የጋዛ ሰርጥ እንድታስወጣ” ትዕዛዝ እንዲሰጡ ነው የጠየቀችው።

‘የአለም አቀፉ ፍርድ ቤት በሁለቱ ቀናት ውሎው ‘የዘር ማጥፋትን የሚመለከተውን እና በ1949 የጸደቀውን ስምምነት ጥሳለች’ በሚል እስራኤል በደቡብ አፍሪቃ የቀረበባትን ክስም ተመልክቷል።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG