ዋሺንግተን ዲሲ —
በሁከት በታመሰችው የምሥራቅ አፍጋኒስታን ክፍለ ሃገር ኩናር ውስጥ “የእስልምና መንግሥት” ብሎ ራሱን የሚጠራው ቡድን ያገታቸውን ሁለት ሲቪሎች መቅላቱን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ገለጡ።
የክፍለ ሃገሩ አገረ ገዢ ዋሂዱላህ ካሊምዛይ ዛሬ ለቪኦኤ በሰጡት ቃል እንደገለጡ “አይኤስ” ሰዎቹን አንገታቸውን ቀልቶ የገደላቸው ማኖጎኢ የምትባለው ወረዳ ውስጥ ነው።
የአፍጋኒስታኑ የእስላማዊ መንግሥት ኮራዛን ቅርንጫፍ ሰዎቹን የአሜሪካ ሰላዮች ናቸው ብሎ ወንጅሎ የቀላሁ እኔ ነኝ ሲል አረጋግጧል።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ