ዋሽንግተን ዲሲ —
የፊታችን ዕሁድ መስከረም 21 በቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ ኃይቅ የሚከበረው የኦሮሞ ማኅበረሰብ የባህልና የምስጋና በዓል የሆነው “እሬቻ” በዓል ያለማንም ጣልቃ ገብነት ሕዝባዊ በዓል ሆኖ እንዲከበር መወሰኑንና የትኛውም የታጠቀ ኃይል ሕዝቡ መካከል እንዳይገባ መወሰኑን አባ ገዳዎች አስታወቁ።
በመድረኩ ላይም ምርቃትና ንግግር የሚያደርጉት አባ ገዳዎች ብቻ ናቸው ብለዋል። የዛሬ ዓመት በተከበረው የእሬቻ በዓል ላይ የበርካቶች ሕይወት መጥፋቱ ይታወሳል።
የጽዮን ግርማን ዝርዝር ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ