በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኢራቅ ኃይሎች ከሶሪያ“የእስልማዊ መንግሥት ነኝ” ባዩ ቡድን ተዋጊዎችን ለማጥፋት ጥቃት ከፈቱ


ፎቶ ፋይል
ፎቶ ፋይል

የኢራቅ መንግሥት ኃይሎች ከሶሪያ ጋር በሚያዋስነው በረሃማ አካባቢ የቀሩትን “የእስልማዊ መንግሥት ነኝ” ባዩ ቡድን ተዋጊዎች ለማጥፋት ዛሬ ጥቃት ማካሄዳቸውን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታወቁ።

የኢራቅ መንግሥት ኃይሎች ከሶሪያ ጋር በሚያዋስነው በረሃማ አካባቢ የቀሩትን “የእስልማዊ መንግሥት ነኝ” ባዩ ቡድን ተዋጊዎች ለማጥፋት ዛሬ ጥቃት ማካሄዳቸውን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታወቁ።

ጦር ሰራዊቱ ባወጣው መግለጫ የኢራቅ ጦር ሰራዊትና የሺያዎች ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ኃይሎች ተዋጊዎች ስፋት ባለው የድንበሩ አካባቢ የቀሩትን የአይሲስ ርዝራዦች መንጥሮ ለማጥፋት በተከፈተው ዘምቻ መካፈላቸውን አመልክቷል።

የኢራቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይደር አል ኣባዲ ማክሰኞ ዕለት በሰጡት መግለጫ ቡድኑ በውጊያው ተሸንፉል፣ ነገር ግን ከበረሃው ውስጥ ጨርሾ ሳይወገድ ድል አድርገናል ብለን አናውጅም ማለታቸው ይታወሳል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG