በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሥልጣናቸውን ለቀቁ


የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሃመድ ዛቫድ ዣሪፍ
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሃመድ ዛቫድ ዣሪፍ

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሃመድ ዛቫድ ዣሪፍ ሥልጣናቸውን በፈቃዳቸው ለቀቁ። ሃገራቸው ከስድስት የዓለም ሃያላን ጋር የደረሰችው የኒውክሊየር ጉዳይ ሥምምነት ዋናው ቀያሽ የነበሩት ዣሪቭ ሥልጣናቸውን እንደሚለቁ በድንገት ይፋ ባደረጉበት መግለጫቸው "ልቀጥል ባለመቻሌ አዝናለሁ" ብለዋል።

ከሥልጣናቸው እንዲሰናበቱ ያስወሰናቸው ምክንያት ምን እንደሆነ ሚኒስትሩ አልገለጹም። ፕሬዚዳንቱ ሃሰን ሩሃኒም ምላሽ አልሰጡበትም።

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፔዎ ግን ሃገራቸው የኢራኑ ሚኒስትር ሥራ መልቀቅ ውሳኔ መፅናት አለመፅናት እስኪለይ እየጠበቀች ናት ብለዋል።

ለማንኛውም እሳቸውና ሃሰን ሩሃኒ የምግብረ ብልሹ ሃይማኖታዊ ማፊያ ፊት ፊት የሚያስቀድማቸው ቢሆኑም ውሳኔውን ሁሉ የሚሰጡት ኻሚኒ መሆናቸውን እናውቃለን ያሉት ፖምፔዎ የኛ ፖሊሲ አልተቀየረም፣ አገዛዙ የጤናማ ሃገር ባህሪ መያዝና ህዝቡን ማክበር አለበት ብለዋል፡፡

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG