በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኢትዮጵያ ውስጥ ሦስት ሚሊየን ተኩል ሰው ተፈናቅሏል


ኢትዮጵያ ውስጥ ሦስት ሚሊየን ተኩል ሰው ተፈናቅሏል
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:45 0:00

ኢትዮጵያ ውስጥ ሦስት ሚሊየን ተኩል ሰው ተፈናቅሏል

ኢትዮጵያ ውስጥ ወደ ሦስት ሚሊየን አምስት መቶ ሺህ የሚጠጋ ቁጥር ያለው ሰው መፈናቀሉን ዓለምአቀፉ የፍልሰት ድርጅት /አይኦኤም/ አስታወቀ።

ድርጅቱ ባለፉት ነኀሴና መስከረም ባካሄደው ዳሰሳ ከሁለት ሚሊየን ተኩል በላይ የቀድሞ ተፈናቃዮች ወደየቀዬአቸው መመለሳቸውን ገልጿል።

አሁን ተፈናቅለው ከሚገኙት 64 ከመቶዎቹ ግጭቶችና ሁከት ያባረሯቸው መሆናቸውን ስለ ሪፖርቱ ለአሜሪካ ድምፅ ማብራሪያ የሰጡት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ቃል አቀባይ ኬ ቪራይ አማራ ክልል ውስጥ ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት አብዛኛው የክልል አካባቢ በአዲሱ ጥናት አለመካተቱን ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ተፈናቃዮቹም ተመላሾቹም አሳሳቢ ችግሮች እንዳሉባቸው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ባለሥልጣን እንጉዳይ መስቀሌ ለቪኦኤ ገልፀዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ፡፡

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG