በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኢንዶኔዥያ ፓርላማ አፈ-ጉባዔ፣ የ$170 ሚሊዮን ስጦታ ተቀብለዋል በሚል በቁጥጥጥ ሥር ዋሉ


የኢንዶኔዥያ ፓርላማ አፈ-ጉባዔ፣ ሲትዮ ኖቫንቶ
የኢንዶኔዥያ ፓርላማ አፈ-ጉባዔ፣ ሲትዮ ኖቫንቶ

የኢንዶኔዥያ ፀረ-ሙስና መሥሪያ ቤት የሀገሪቱ ፓርላማ አፈ-ጉባዔ፣ የ$170 ሚሊዮን ስጦታ ተቀብለዋል በሚል፣ በቁጥጥጥ ሥር አዋላቸው።ሲትዮ ኖቫንቶ ትናንት ማታ ነው ወደ ወህኒ የተላኩት።

የኢንዶኔዥያ ፀረ-ሙስና መሥሪያ ቤት የሀገሪቱ ፓርላማ አፈ-ጉባዔ፣ የ$170 ሚሊዮን ስጦታ ተቀብለዋል በሚል፣ በቁጥጥጥ ሥር አዋላቸው። ሲትዮ ኖቫንቶ ትናንት ማታ ነው ወደ ወህኒ የተላኩት።

አንድ የፀረ ሙስና መሥሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ እንደገለፀው፣ አፈ-ጉባዔ ኖቫንቶ፣ ጥያቄ እየቀረበለው ለ20 ቀን በእሥር ይቆያሉ።

አፈ-ጉባዔው በሰጡት ቃል ግን፣ ምንም ጥፋት እንዳልፈፀሙ ነው የተናገሩት።

ባለሥልጣናት በበኩላቸው፣ ኖቫስቶ የመንግሥት ገንዘብ የመነተፉት፣ አዲስ የመታወቂያ ወረቅት ለማዘጋጀት ከተሰየመው ቡድን መካከል ሆነው በሚሠሩበት ጊዜ መሆኑን አመልክተዋል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG