. ትንበያዎቹ "የተለያዩ ብቻ ሳይኾኑ ከእውነታውም የራቁ ናቸው" - ባለሞያ
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ)፣ በቅርቡ ስለ ኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት ያወጣው ትንበያ፣ እ.ኤ.አ በ2025፣ 25 ከመቶ መድረሱን ይገልጻል፡፡ የዋጋ ንረቱ አኹን ካለበት ሁለት አኀዝ ወደ ነጠላ አኀዝ ለመውረድ እስከ 2028 ሊቆይ እንደሚችልም አይኤምኤፍ ተንብይዋል፡፡
በአንጻሩ የኢትዮጵያ መንግሥት፣ የዋጋ ግሽበቱ እየወረደ መምጣቱንና አኹን ከ15 እስከ 16 በመቶ ዝቅ ማለቱን ይናገራል፡፡
በለንደን የሚገኙት የፋይናንስ እና የምጣኔ ሀብት ባለሞያ ዶር. አብዱልመናን መሐመድ ሃምዛ ግን፣ የአይኤምኤፍም ኾነ የኢትዮጵያ መንግሥት ቁጥሮች፣ "የተለያዩ ብቻ ሳይኾኑ ከእውነታው የራቁ ናቸው፤" ይላሉ፡፡
ከአሜሪካ ድምፅ ጋራ አጭር ቆይታ ያደረጉት ዶር. አቡዱልመናን፣ በአይኤምኤፍ እና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል ያለውን የትንበያ ልዩነት አብራርተዋል፡፡ ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይይ ይከታተሉ።
መድረክ / ፎረም